Photo credit to:
UNESCO
(The image is retouched by the webmaster)
አብዛኛዎቹ ምሁራን እነደሚስማሙበት ከሆነ፤ለቤተሰባቸው ሦስተኛ ልጅ የሆኑት እቴጌ ጣይቱ የተወለዱት ግንቦት 3 ቀን 1843 ዓ.ም. ነው፡፡
አባታቸው ራስ ብጡል ኃይለማሪያም የየጁና የጎንደር ሰው ናቸው፡፡
እናታቸው ጎጃም ክፍለ ሀገር የተወለዱት ወይዘሮ የውብዳር ይባላሉ፡፡
እቴጌ ጣይቱ በልጅነታቸው አማርኛ ማንበብና መጻፍ ተምረዋል፡፡ በገናም የመደርደር ችሎታ ነበራቸው፡፡
እቴጌ ጣይቱ ግእዝን በደንብ የተረዱ ከመሆናቸውም በላይ፤ የዲፐሎማሲ፣የፖለቲካና የኢኮኖሚ ትምህርትም እንዳገኙ ይታመናል፡፡
የእቴጌ ጣይቱ ወላጆች በጊዚያቸው፤ የጎጃም፣ የየጁ፤ የወሎና የቤገምድር ገዥዎች እንደነበሩ ይነገራል፡፡
የወላጆቻቸው ባላባታዊ የዘር ሐረግ ወደኋላ ሲቆጥር፤ ትውልዳቸው ከጎጃም ከሆነው በ17ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ ነግሠው እስከነበሩት
እስከ አፄ ሱስኒዮስ ዘመነ መንግስት ድረስ ይዘረጋል፡፡
አጎታቸው (የአባታቸው ወንድም) ደጃዝማች ውቤ ኃይለማሪያም የትግራይ ገዥ ነበሩ፡፡
![Etegie Tayitu](image\tayitu-2.jpg)
(The image is retouched by the webmaster)