Content-Language: am አርበኞች ገጽ ሁለት
header image


Ethiopian Patriots


የፋሽስት ኢጣሊያ ወራሪ ጦር በእብሪት ተነሳስሰቶ ከመስከረም 22 ቀን 1928 ዓ.ም. ጀምሮ እሰከ ሚያዝያ 26 ቀን 1933 ዓ.ም ድረስ በኢትዮጵያ ላይ ለሁለተኛ ጊዜ የግፍ ወረራ በፈፀመበት ወቅት ለውድ ሀገራቸው ነፃነት ሲሉ የጀግንነት ተጋድሎ በማድረግ ከተዋደቁት ውድ የኢትዮጵያ ጀግኖች አርበኞች መካከል የጥቂቶቹን ፎቶዎች ከአጫጭር መግለጫዎች ጋር በከፊል የሚያሳይ


ለላፕቶፕ ወይም ለዴስክቶፕ ኮምፒውተር፤ በማውስ ጠቋሚው ፎቶዎችን በመዳሰስ፣
ለስማርት ፎን ከሆነ በጣት በመጫን የፎቶዎችን መግለጫ ማየት ይችላሉ

Major Mesfin Seleshi
ሻለቃ መስፍን ስለሺ (ራስ)
በጀግንነታቸው የታወቁት አርበኛና የጦር መሪ ራስ መስፍን ስለሺ
Major Mesfin Seleshi and Lij Abiy Abebe
ሻለቃ መስፍንና ልጅ አብይ አበበ
በገፈርሳ፣ በሞረትና በክልቤ የአርበኞች ጦርነት ወቅት ከማረኩት መሣሪያዎች ጋር ጀግኖች አርበኞች ሻለቃ መስፍን ስለሺና ልጅ አቢይ አበበ
Ras Bitwadad Makonnen Endalkachew
ራስ ቢተወደድ መኮንን እንዳልካቸው
ራስ ቢተወደድ መኮንን እንዳልካቸው በሸዋ ተጉለት የተወለዱ ሲሆን፤ በኋላም በፋሽስት ኢጣሊያ ወረራ ወቅት በጀነራልነት ማዕረግ ጠላትን ለመዋጋት ከኢሉባቦር ጦር ይዘው የዘመቱ አርበኛ ነበሩ፡፡
Ras Andaregachew Mesay
ራስ አንዳርጋቸው መሣይ
ራስ አንዳርጋቸው መሣይ ንጉሠ ነገሥቱ ጎጃም ከገቡ በኋላ ሞጣ ላይ ተቆርጦ የቀረውን የጠላት ጦር እንዲመቱ ታዘው ሄደው ከአገሩ አርበኞች ጋር በመሆን የጠላትን ጦር ምሽግ ሰብረው ጠላትን ድል አድርገዋል፡፡ በስፍራው የነበረውንም መትረየስ ይዘው ወደ ንጉሠ ነገሥቱ ተመልሰዋል፡፡
Ras Bitewoded Tessema Nadew
ራስ ቢተወደድ ተሰማ ናደው
ራስ ቢተወደድ ተሰማ ናደው የኢሊባቦርን ጦር ይዘው አድዋ ዘምተው ፋሽስት ኢጣሊያን የተዋጉ እና የልጅ እያሱ ባለሙሉ እንደራሴ ሆነው በምኒልክ ከተሾሙ በኋላ በሕመም ምክንያት ሕይዎታቸው ያለፈ
Ras Hailu Belew
ራስ ኃይሉ በለው
ራስ ኃይሉ በለው በጎጃም ጠቅላይ ግዛት በብቸና አውራጃ ዙሪያ የነበሩ የአርበኞች መሪ ሲሆኑ ከእርሳቸውም ጋር ቀኛዝማች ሽፈራው ረታ፣ ቀኛዝማች አበሻ ጀሌና ልጅ ደበበ ወዳጄ ነበሩ፡፡
Lij Hailemariam Mamo
ራስ ወልደ ጊዮርጊስ አቦዬ
ራስ ወልደ ጊዮርጊስ አቦይ የንጉሥ ሳህለ ሥላሴ የልጅ ልጅ፣ የዳግማዊ ምኒልክ የቅርብ ዘመድ ሲሆኑ፤ 8,000 ሠራዊታቸውን አሰልፈው ዓድዋ የተዋጉ አርበኛ ናቸው።
Bitewoded_Mekonnen_Demesew
ቢተወደድ መኮንን ደምሰው
ቢተወደድ መኮንን ደምሰው በማይጨው ጦር ግንባር ተሰልፈው ለተከታዩ ትውልድ አኩሪ ታሪክ የተውለት ከእውቅ የአርበኞች መሪ አንዱ ነበሩ፡፡
Bitewoded Ayalew Mekonen
ቢተወደድ አያሌው መኮንን
ቢተወደድ አያሌው መኮንን በጎጃም ጠቅላይ ግዛት አቸፈር በተባለው ቦታ የአርበኞች መሪ የነበሩ
Dejazmach Abera Kasa
ደጃዝማች አበራ ካሣ
ከማይጨው ተመልሶ የመጣውንና በየሥፍራው የሚገኘውን ሕዝብ ጠርተው፤ ”የአርበኝነትን ሙያ በመመሥረት ከፋሽት ወታደሮች ጋር አዋግተሀል“ በመባል ከወንድማቸው ከደጃዝማች አስፋወሰን ካሣ ጋር ሕይዎታቸው በግፍ ያለፈ
Dejazmach Asfawesen Kasa
ደጃዝማች አስፋወሰን ካሣ
ከማይጨው ተመልሶ የመጣውንና በየሥፍራው የሚገኘውን ሕዝብ ጠርተው፤ ”የአርበኝነትን ሙያ በመመሥረት ከፋሽት ወታደሮች ጋር አዋግተሀል“ በመባል ከወንድማቸው ከደጃዝማች አበራ ካሣ ጋር ሕይዎታቸው በግፍ ያለፈ
Dejazmach Desta Shewarekabeh
ደጃዝማች ደስታ ሸዋ እርካብህ
“ለነዚህ ደም አብርሮ ላመጣቸው ዕውራን ፋሽስቶች ጥይታችንን አናባክንም” በማለት
ተራራ ላይ ወጥተው በናዳ ማዕበል ጠላትን ያስቀሩ ደጃዝማች ደስታ ሸዋእርካብህ እኝህ ነበሩ፡፡
Dejazmach Geleta Qoricho
ደጃዝማች ገለታ ቆሪቾ
የመርሐቤቴና ያካባቢው ስመ ጥሩ ጀግና ደጃዝማች ገለታ ቆሪቾ
Dejazmach Demesie Woldeamanuel
ደጃዝማች ደምሴ ወልደአማኑኤል
የአርበኝነት ተግባራቸውን ከልጅ ኃይለማሪያም ማሞ እና ከራስ አበበ አረጋይ ጋር የፈጸሙና በኋላም “የአርበኞች ሐዋርያ” በመባል የታወቁት ቆራጡ ጀግና ደጃዝማች ደምሴ ወልደአማኑኤል እኝህ ነበሩ፡፡
Dejazmach Yilma Beshe Fitawurari Shewareged Beshe
ለማ በሸ እና ሸዋረገድ በሸ
ወንድማማች አርበኞች ደጃዝማች ይልማ በሸ እና ፊታዉራሪ ሸዋረገድ በሸ
Dejazmach Tsehayu Enquselassie
ደጃዝማች ፀሐዩ ዕንቆ ሥላሴ
ደጃዝማች ፀሐዩ ዕንቆ ሥላሴ የጀግንነት ሙያ “ጎርፎ” ተብሎ በሚጠራው የውጊያ ቦታ ላይ ከጠላት ጋር በተደረገው ጦርነት በመትረየስ በርካታ ጠላትን የደመሰሱ አርበኛ ናቸው
Dejazmach Wolde Mariam
ደጃዝማች ወልደ ማሪያም
በደብረ ብርሃን ዋዩ ቀበሌ የተወለዱት፤ ደጃዝማች ወልደ ማሪያም፤ በአድዋ ዘመቻም የተዋጉና በኋላም በማይጨው ዘመቻ ጊዜም በገሙ ጎፋ ግዛት ለነበረው የጦር አለቃ ሆነው የተዋጉ አርበኛ ነበሩ፡፡
Dejazmach Zewde Asfaw
ደጃዝማች ዘውዴ አስፋው
ደጃዝማች ዘውዴ አስፋው በፋሽሰት ኢጣሊያ ወረራ ወቅት ባሳዩት ከፍተኛ የአርበኝነት ሙያ ለጠላት አስጊ መሆናቸውን በማወቅ ግራዚያኒ ልብ የሚማርክ ደብዳቤ እየጻፈ እንዲገቡለት ቢጠይቃቸውም ተስፋ የሚያስቆርጥ መልስ እየሰጡ በቆራጥነትና በታማኝነት ተዋግተው ክብር ያገኙ ሀገር ወዳድ አርበኛ ነበሩ፡፡
Dejazmach Abebe Damtew
ደጃዝማች አበበ ዳምጠው
ደጃዝማች አበበ ዳምጠው በማይጨው ጦርነት ወቅት የጎፋና የባኮ ጦር በሙሉ የጦር አዝማች የበሩ
Dejazmach Takele Woldehawariat
ደጃዝማች ታከለ ወልደ ሐዋርያት
ሀገራቸውንና ወገናቸውን ከልብ የሚወዱ፣ በአምስቱ የጠላት ዘመን በዱር በገደል እየተዘዋወሩ የፋሽስትን ወታደሮች ያራውጡ ታላቅ አርበኛ ነበሩ፡፡
Dejazmach Kefelew Woldetsadik
ደጃዝማች ከፈለው ወልደ ጻድቅ
ደጃዝማች ከፈለው ወልደ ጻድቅ የመንዝ ማኅፀነ ምድር ካፈራቻቸው ጀግኖች ልጆቿ መካከል አንዱ ነበሩ፡፡
Dejazmach_Zewudu_Abakoran
ደጃዝማች ዘውዱ አባኮራን
Dejazmach Kebede Kasa
ደጃዝማች ከበደ ካሣ
በከሰም በረሀ የድንጋይ መዝጊያ በመሆን ጠላትን ያርበደብዱ የነበሩት ደጃዝማች ከበደ ካሣ እኝህ ነበሩ፡፡
Dejazmach Gebremariam Belanka
ደጃዝማች ገብረ ማሪያም በላንቃ
በማይጨው ጦርነት ከንጉሠ ነገሥቱ ጋር ለመዝመት ጉዞ የጀመሩት ደጃዝማች ገብረ ማሪያም በላንቃ፤ እስከመጨረሻው ድረስ በመዋጋት ጠላትን ካጠቁ በኋላ በጦር ሜዳ ላይ ሲዋጉ የተገደሉ ጀግና የጦር መሪ ነበሩ፡፡
Dejazmach Wolde Amanuel Hawas
ደጃዝማች ወልደ አማኑኤል ሀዋስ
ደጃዝማች ወልደ አማኑኤል ሀዋስ በማይጨው ጦርነት ከንጉሠ ነገሥቱ ሳይለዩ ግዳጃቸውን በጥሩ ሁኔታ የፈጸሙ ሲሆን፤ ሰው ሁሉ የሞራል ውድቀት ደርሶበት በነበረበት ጊዜ ሁሉ በጎደለው ቦታ ሁሉ በመገኘት ጉዞውን ከመሩት ውስጥ በአንደኝነት ይጠቀሱ የነበሩ ሰው ናቸው፡፡
Dejazemach Gillla Giorgis
ደጃዝማች ጊላ ጊዮርጊስ
ደጃዝማች ጊላ ጊዮርጊስ፤ በአገውና በዳሞት በአራቱ የአርበኘነት ዘመን ጥሩ አገልግሎት የሰጡ አርበኛ ነበሩ
Dejazmach Mengesha Jembere
ደጃዝማች መንገሻ ጀንበሬ
ደጃዝማች መንገሻ ጀንበሬ በጎጃም ጠቅላይ ግዛት ጉታ በተባለው ቀበሌ የአርበኞች መሪ የነበሩ
Dejazmach Negash bezabeh
ደጃዝማች ነጋሽ በዛብሀ
ደጃዝማች ነጋሽ በዛብሀ በጎጃም ጠቅላይ ግዛት ወንበርማ በተባለው ስፍራ ከ 500 ጦር በላይ አሰልፈው የጠላትን ጦር መግቢያ መውጫ ያሳጡ አርበኛ ነበሩ፡፡
Dejazmach Baheta Hagos
ደጃዝማች ባሕታ ሃጎስ
ከጣሊያኖች ጋር ተስማምተው ይሰሩ ከነበሩት፤ ራስ መንገሻ ዮሃንስ፤ ራስ አሉላና ባሕታ ሃጎስ ወደ አዲስ አበባ ሄደው ምኒልክን ይቅራታ ጠይቀው ከተመለሱ በኋላ፤ ባሕታ ሃጎስ 1,500 ጦር ይዘው የኤርትራ ፋሽስት ኢጣሊያን ጦር ከሰገነይቲ ለማሶጣት ከራስ መንገሻ ዮሃንስ ጋር ተቀናጅተው ውጊያ ለመክፈት አመቻቹ፡፡ ጊዜ ለመግዛት ሲሉም ከአስመራ የተዘረጋውን የቴሌግራም ሽቦ በመበጣጠስ የጣሊያኖችን ምሽግ ለማስለቀቅ ሲሞክሩ የሻለቃ ቶዞሊ ጦር ደርሶ በተከፈተው ውጊያ ላይ የተገደሉ ጀግና ናቸው፡፡
Weyzero Welete Amanuel Papatakis
ወይዘሮ ወለተ አማኑኤል ፓፓታኪስ
ከዝነኛዋ አርበኛ ከወይዘሮ ሸዋረገድ ገድሌ ጋር በመተባበር ለአርበኞች ስንቅና ልብስ በማቀበል ያገለገሉ የውስጥ አርበኛ ነበሩ፡፡
Woyzero Zewuditu Gizaw
ወይዘሮ ዘውዲቱ ግዛው
ጾዎታዋ ሳይገድባት ከወንድ አርበኞች ጋር እኩል ተሰልፋ የተዋጋች የመንዝና የተጉለት አርበኛዋ ወይዘሮ ዘውዲቱ ግዛው
Weyzero Lakech Demesew
ወይዘሮ ላቀች ደምሰው
ጾዎታዋ ሳይገድባት ከወንድ አርበኞች ጋር እኩል ተሰልፋ የተዋጋች የወሎ አርበኛዋ ወይዘሮ ላቀች ደምሰው
Weyzero Lakech Demesew
የአርሲዋ ወይዘሮ በላይነሽ
ጾዎታዋ ሳይገድባት ከወንድ አርበኞች ጋር እኩል ተሰልፋ የተዋጋች ኢትዮጵያዊ አርበኛዋ የአርሲዋ ወይዘሮ በላይነሽ
Weyzero Lakech Demesew
ወይዘሮ አየለች
ጾዎታዋ ሳይገድባት ከወንድ አርበኞች ጋር እኩል ተሰልፋ የተዋጋች ኢትዮጵያዊ አርበኛዋ ወይዘሮ አየለች
Weyzero Lakech Demesew
ወይዘሮ ቆንጅት አብነት
ጾዎታዋ ሳይገድባት ከወንድ አርበኞች ጋር እኩል ተሰልፋ የተዋጋች ኢትዮጵያዊ አርበኛዋ ወይዘሮ ቆንጅት አብነት
Weyzero Lakech Demesew
የቡልጋዋ ወይዘሮ በላይነሽ
ወይዘሮ በላይነሽ፤ ለኢትዮጵያ ነፃነት ስትል ከሌሎች አርበኞች ጋር ሆኗ ወራሪውን ፋሽስት ኢጣሊያን የታገለች የሴት አርበኛ ነበረች፡፡
Weyzero Lakech Demesew
የቤገምድሯ ወይዘሮ ከበደች ደሴ
ወይዘሮ ከበደች ደሴ፤ ለኢትዮጵያ ነፃነት ስትል ከሌሎች አርበኞች ጋር ሆኗ ወራሪውን ፋሽስት ኢጣሊያን የታገለች የሴት አርበኛ ነበረች፡፡
Weyzero Lakech Demesew
ጎጃሜዋ ወይዘሮ ብርሀኔ ገዛኸኝ
ጃሜዋ የብቸና ልጅ ወይዘሮ ብርሀኔ ገዛኸኝ ለኢትዮጵያ ነፃነት ስትል ከሌሎች አርበኞች ጋር ሆኗ ወራሪውን ፋሽስት ኢጣሊያን የታገለች የሴት አርበኛ ነበረች፡፡
Weyzero Lakech Demesew
ወይዘሮ ይደነቁ ተሰማ
ወይዘሮ ይደነቁ ተሰማ፤ ለኢትዮጵያ ነፃነት ስትል ከሌሎች አርበኞች ጋር ሆኗ ወራሪውን ፋሽስት ኢጣሊያን የታገለች የሴት አርበኛ ነበረች፡፡
Weyzero Lakech Demesew
ወይዘሮ ማንአለብሽ ደባልቄ
የሰሜን ሸዋዋ ወይዘሮ ማንአለብሽ ደባልቄ፤ ለኢትዮጵያ ነፃነት ስትል ከሌሎች አርበኞች ጋር ሆና ወራሪውን ፋሽስት ኢጣሊያን የታገለች የሴት አርበኛ ነበረች፡፡
Weyzero Lakech Demesew
ወይዘሮ አየለች ዮሴፍ
ወይዘሮ አየለች ዮሴፍ፤ ለኢትዮጵያ ነፃነት ስትል ከሌሎች አርበኞች ጋር ሆና ወራሪውን ፋሽስት ኢጣሊያን የታገለች የሴት አርበኛ ነበረች፡፡
Weyzero Lakech Demesew
የባሌ ጎባዋ ወይዘሮ በላይነሽ
ወይዘሮ በላይነሽ፤ ለኢትዮጵያ ነፃነት ስትል ከሌሎች አርበኞች ጋር ሆኗ ወራሪውን ፋሽስት ኢጣሊያን የታገለች የሴት አርበኛ ነበረች፡፡
Weyzero Lakech Demesew
ወይዘሮ ቀለመወረቅ ጥሩነህ
ወይዘሮ ቀለመወረቅ ጥሩነህ የአርበኝነት ሙያውን ከባለቤቷ በመውሰድ የደፈጣ ውጊያውን በባሌና አርሲ ስታከናውን ቆይታ በመጨረሻም ባለቤቷ ሀገሩን ከድቶ ወደ ጣሊያን ሲገባ እርሷም ከባለቤቷ ተለያይታ በስደት ወደ ኬንያ ተጉዛለች፡፡
Weyzero Lakech Demesew
የላስተዋ ወይዘሮ ሸዋነሽ አብርሃ
የላስተዋ ወይዘሮ ሸዋነሽ አብርሃ፤ ሴት ልጇን ለልጅ እያሱ ልጅ ለሆነው ለዮሐንስ እያሱ በመዳሯ ምክንያት ብዙ ተከታይ አርበኞችን ያፈራች የሴት ጀግና ስትሆን፤ አርበኛው ባለቤቷ በ1929 ዓ.ም. በጦር ሜዳ ሲሰዋ ስትመለከት አላስችል ብሏት ህፃን ልጇን በመያዝ የባለቤቷን የመሪነት ቦታ ተክታ የተዋጋች ጀግና የነፃነት አርበኛ ነች፡፡
Weyzero Lakech Demesew
የደጃዝማች ሀብተ ሚካኤል ባለቤት
ስሟ ያልታወቀው ተዋጊ ጀግና ሴት፤ በሶማሊያና በኬንያ ድንበር አጠገብ በሚገኘው ዶሎ በተባለው ሥፍራ የጦር አዛዥ የነበሩት የደጃዝማች ሀብተ ሚካኤል ሚስት ነበረች። ደጃዝማች ሀብተ ሚካኤል ምሽጋቸው ውስጥ ሆነው የጠላትን መምጣት ሲጠባበቁ ሚስታቸው ግን በፍጥነት በአካባቢ ወደአለው ኮረብታ ላይ ወጥታ ስታይ የኢጣሊያ ወታደሮች መምጣታቸውን ተመለከተች፡፡
ባለቤቷ ጦራቸውን ይዘው ተንቀሳቅሰው ጠላትን እንዲወጉ ብትነግራቸውም ሀሳቧን ሊቀበሏት ስላልፈለጉ በእራሷ ተነሳሽነት 150 ወታደሮችን ይዛ ጠላት ገና ምሽጉ ጋ ሳይደርስ በጠላት ላይ ፈጣን ጥቃት በመሰንዘር ብዙ የጠላት ወታደሮችን ገድላ፤ ብዙ የጦር መሣሪያና ጥይቶችን ማርካለች፡፡
ባል ሲያመነታ ሚስት ቆራጥ እርምጃ መውሰዷ በታሪክ አጋጣሚዎች እንደ አንዱ ሊወሰድ የሚችል አኩሪ ገድል ነው፡፡
Weyzero Lakech Demesew
ወይዘሮ ልኬለሽ በያን
ጾወታዋ ሳይገድባት ከወንድ አርበኞች ጋር እኩል ተሰልፋ በደፈጣ ውጊያ የራሷን ተዋጊዎች እየመራች ፋሽስት ጣሊያንን እየተዋጋች ሳለ ፋሽስቶች በጣሉት የአይሮፕላን ቦምብ የተነሳ ከባድ አደጋ ደርሶባት በአንድ ትንሽ ጎጆ ውስጥ ተኝታ እየተሰቃየች ነበር፡፡ ጀግናዋ የማይጨው አርበኛ ሁኔታውን ስትገልጽ፤ የፋሽስት ወታደር አውቄ የተኛሁ መስሎት በያዘው መሳሪያ በሰደፉ ትከሻየ ላይ መታኝ፡፡” ብላለች፡፡
ከዚያ በኋላ በጠላት ከነልጇ ተማርካ እስከነፃነት ድረስ ከአንድ አመት በላይ ታስራ የተሰቃየች ቆራጥ አርበኛ ነበረች፡፡
Leutenat General Merid Mengesha
ጀነራል መርድ መንገሻ
Major General Tedela Mekonen
ሜጀር ጀነራል ተድላ መኮንን
የጥንታዊት ኢትዮጵያ የጀግኖች ማኅበር መሥራች አባል የነበሩና በአርበኝነት ዘመን በሸዋ ክፍለ ሀገር ከራስ አበበ አረጋይ ጋር በመሆን ጠላትን ያስጨነቁ አርበኛ እኝህ ነበሩ፡፡
Brigader General Woldeyohanes Teklu
ጀነራል ወልደ ዮሐንስ ተክሉ
በወታደርነት ሙያው ከህጻንነት ጊዜው ጀምሮ መደነቅን ያተረፈ፣ በጠላት ወረራ በዱር እየተዘዋወረ ጠላትን ያሽቆጠቁጥ የነበረው ባጭር ታጣቂው ብርጋዴር ጀነራል ወልደዮሐንስ ተክሉ ይህ ነበር፡፡
Fitawurari Tesema Eregete
ፊታውራሪ ተሰማ እርገጤ
ፊታውራሪ ተሰማ እርገጤ በአምስቱም የጠላት ወረራ ዘመን በሸዋ ጠቅላይ ግዛት በመንዝና ይፋት አውራጃ ከፍ ባለ ጀግንነትና ቆራጥነት ጠላትን ሲያርበደብድና ድል ሲያደርግ የነበረ ሰመ ጥሩ አርበኛ ነበር፡፡
Colonel Dejenie Woldie
ኮሎኔል ደጀኔ ወልዴ
የቡልጋው አርበኛ ኮሎኔል ደጀኔ ወልዴ እኝህ ነበሩ፡፡
Colonel Worku Ayele
ኮሎኔል ወርቁ አየለ
ኮሎኔል ወርቁ አየለ የክብር ዘበኛ አባል ሲሆን በአምስቱ የጠላት ወረራ ዘመን በራስ መስፍን ስለሽ ስር በሚመሩት አርበኞች ውስጥ ሆኖ በጎሾ በኩል የነበረውን የጠላት ጦር ለመውጋት በተሰማሩበት ጊዜ ግንባር ቀደም ጦር ሆኖ ቡኖ በደሌ ላይ ከፍ ያለ ድል ያስገኘ ስመ ጥሩ አርበኛ ነበረ፡፡
Major Desalegne Tekelewold
ሻለቃ ደሻለኝ ተክለወልድ
ከገፈርሳ ጦርነት ጀምረው ጠላትን የተቋቋሙና ከልጅ ኃይለማሪያም ማሞ በኋላም ከራስ አበበ አረጋይ ጋር ሆነው በጀግንነት አገልግለዋል፡፡
Shaleka Haile Selassie Belayneh
ሻለቃ ኃይለሥላሴ በላይነህ
ህሊናው ባልረባ ወሬ የማይረበሽ በመሆኑ ይህን ተግባር አስተባብሮ በመያዙ ለሀገሩ በቆራጥነት ያገለገለው የስመ ጥሩው አርበኛ የፊታውራሪ ተወንዴ በላይነህ ታላቅ ወንድም ሻለቃ ኃይለሥላሴ በላይነህ ይህ ነበር፡፡
Shambel Semie Abdi
ሻምበል ስሜ አበዲ
የቡልጋ አርበኛ የነበረ
Meto Aleka Sahele Enquselassie
መቶ አለቃ ሳህሌ እንቁ ሥላሴ
በ 1929 ዓ.ም እነዋሪ ላይ በተደረገው ከባድ ጦርነት ላይ በጦር ሜዳ በጀግንነት የወደቀ
Yemeto Aleka Kebede Yeshigetta
መቶ አለቃ ከበደ የሽጌታ
ከነልጅ በየነ አስቤና ከነልጅ አየለ አስቤ ጋር የተጉለት አርበኞች መሪ በመሆን በጠላት ላይ ከባድ ጉዳት አድርሰዋል፡፡
Lij Wosen Hailu
ልጅ ወሰን ኃይሉ
ሞጣ ላይ ተቋርጦ የቀረ የጠላት ጦር ስለነበረ፤ ልጅ ወሰን ኃይሉና ልጅ አንዳርጋቸው መሣይ ጠላትን እንዲወጉ ታዘው ሄደው ሞጣ ከሚገኙት አርበኞች ጋር በመሆን የጠላትን ምሽግ በመስበር ጠላትን ድል አድርገው ብዙ የጠላት ምርኮኞችንና መትረየሶችን ማርከው ጎሐጽዮን ድረስ ያመጡ ጀግና አርበኛ ነበሩ፡፡
Lij Abere Yemam
ልጅ አበረ ይማም
ልጅ አበረ ይማም ከፍታውራሪ ተገኔ ጋር በመሆን በጎጃም ጠቅላይ ግዛት የዳሞት ክፍል የጉታ አገረ ገዥ በነበሩበት ጊዜ ጠላት አገሩን ሲይዝ ሀገሩ እርሳቸው እንነዲመሯቸው በጠየቀው መሠረት ጥያቄውን ተቀብለው የአርበኞች መሪ በመሆን ባህርዳር ላይና በርካታ ቦታ ጠላትን ያጠቁ አርበኛ ሲሆኑ የጦር ጓዳቸው ፍታውራሪ ተገኔ በውጊያ ላይ ሞተዋል፡፡
Lij Seifu Abawollo
ልጅ ሰይፉ አባወሎ
ልጅ ኃይለማሪያም ማሞ በሞቱበት ዕለት በጀግንነት ሲዋጋ የቆሰለ
Lij Gizachew Haile
ልጅ ግዛቸው ኃይሌ
እጅግ ከታወቁትና ምርጥ ከሆኑት አርበኞች መካከል በውጊያ ላይ በጠላት ተመቶ የወደቀ
Lij Gerbi Bulto
ልጅ ገርቢ ቡልቶ
ከጀግንነት ሙያው በላይ የሜታ ተወላጅና ባላባት እንደመሆኑ መጠን ለአርበኞቹ ምግብና መጠጥ በማቅረብ ብዙ ጊዜ የረዳ በመሆኑ ሊደነቅ ይገባል፡፡ በፎቶው ላይ አጠገቡ የሚታዩት ባለቤቱ ወይዘሮ አበባ በላቸው ሲሆኑ እርሳቸውም በበኩላቸው ከባላቸው ሳይለዩ በአርበኝነት ያገለገሉ ናቸው፡፡ እኝህ ሴት ከጠላት ጋር ሲዋጉ ሻንቆ የተባለው መትረየስ ተኳሽ ተመቶ ሲወድቅ እርሱን ቀና አድርገው ጥግ ካሲያዙ በኋላ መትረየሱን ራሳቸው ይዘው እየተኮሱ ብዙ የፋሽስት ወታደሮቸን የጨረሱ በመሆናቸው ታሪክ ሲያስታውሳቸው ይኖራል፡፡
Lij Emaelaf Heruy
ልጅ እማዕላፍ ህሩይ
ከጠላት ወገንም ሆነ ከአርበኞቹ በኩል እየተተኮሱ የሚወድቁትን የጥይት ቀለሆች እየለቀመ ባሩዱን ከአንዱ ወደሌላው በማቀናነስ እየሠራ በጊዜው የነበረውን የጥይት ችግር ያቃለለና የውጅግራ እርሳስ እያቀለጠ ማኅተም ሠርቶ ፓምፍሌቶችን እያዘጋጀ “ከግርማዊነታቸው የተላከ ነው” በማለት ለአርበኞችና ለባላገሩ ሕዝብ የሰበከ አርበኛ ነበር፡፡
Lij Chernet Teklewold
ልጅ ቸርነት ተክለወልድ
ለሀገርህ ትሠራለህ ተብሎ በወንጀል ታስሮ የሞት ፍርድ ከተበየነበት በኋላ የሞት ጽዋውን የሚቀበልበትን ጊዜ የሚለይ ተራ ቁጥር (404) በማጅራቱ ላይ ታስሮበት ይታያል፡፡
Lij Kifle Enquselasie
ልጅ ክፍሌ ዕንቁሥላሴ
ከአባትና ከወንድም ሞት የሀገር ሞት ይብሳል በሚል ዓላማ ሕሊናው ተመርዞ ጠላትን እየተዘዋወረ ያጠቃ የነበረ አርበኛ ነበር፡፡
Lij Teferi Antenyesmu
ልጅ ተፈሪ አንተንይስሙ
በያዘው ረዥም ለበን ጠመንጃ ጠላቱን እያራወጠ አልቤን ጠመንጃና ምንይሽር ጠመንጃ የማረከ ጀግና
Lij Zewude Antenyesmu and Lij Denke Antenyesmu
ዘውዴ አንተንይስሙና ደነቀ አንተንይስሙ
ሁለቱም ወንድማማቾች ዘውዴ አንተንይስሙና ልጅ ደነቀ አንተንይስሙ የተጉለት አርበኞች ነበሩ፡፡
Lij Wodemagnehu Setaregew
ልጅ ወንድማገኘሁ ሰጥ አርገው
ልጅ ወንድማገኘሁ ሰጥ አርገው በቤገምድር ጠቅላይ ግዛት በማሕበረ ሥላሴ አቅራቢያ ቻባ በተባለ ቀበሌ የሚገኝ ሲሆን ወደ ጎጃም ቀዳሚ ሆኖ ለሚገባው መላክተኛ ጦር መንገድ በመምራት በታማኝነትና በቅንነት ያገለገለ አርበኛ ነበር፡፡
Fitawurari Alemayehu Goshu
ፊታውራሪ አለማየሁ ጎሹ
በዐድዋ ጦርነት አርበኛ የነበሩና በወልወሉ ግጭት ወቅት በዊጊያ መስዋእት የሆኑት ጀግናው ፊታውራሪ አለማየሁ ጎሹ፡፡
Kegnazemach Worku Seneke
ፊታውራሪ ወርቁ ስንቄ
ፊታውራሪ ወርቁ ስንቄ በቋራ ግዛት የነበሩ ስመ ጥሩ አርበኛ ሲሆኑ፤ ከንጉሠ ነገሥቱ ወደ አርበኞች፤ ከአርበኞች ወደ ንጉሠ ነገሥቱ መልዕክት ይላላኩ የነበሩት መልዕክተኞች ችግር እንዳይደርስባቸው ይረዱ የነበሩ አርበኛ ነበሩ፡፡
Fitawurari Haile Eyesus Felate
ፊታውራሪ ኃይለ እሱስ ፈላቴ
ፊታውራሪ ኃይለ እሱስ ፈላቴ በጎጃም የደጋ ዳሞት አርበኞች መሪ የነበሩና ጠላትን መቆሚያ መቀመጫ ያሳጡ የነበሩ እውቅ አርበኛ ናቸው፡፡
Fitawurari Admasu Alemu
ፊታውራሪ አድማሱ ዓለሙ
ፊታውራሪ አድማሱ ዓለሙ በጎጃም ደብረማርቆስ አካባቢ የጠላትን ጦር በጀግንነት የተዋጉ አርበኛ ናቸው፡፡
Fitawurari Ayalew Desta
ፊታውራሪ አያሌው ደስታ
ፊታውራሪ አያሌው ደስታ በጎጃም ደብረማርቆስ አካባቢ ጠላትን በጀግንነት ይዋጉ የነበሩ አርበኛ ናቸው፡፡
Fitawurari Haile Aba Meresa
ፊታውራሪ ኃይሌ አባመርሳ
የገንዘብ ሚኒስትር የነበሩት በጅሮንድ ፍቅረ ሥላሴ፤ መዋጋታችንን ትተን እጃችንን ለጠላት እንስጥ ሲሉ፤ አርሲ ለይ የተገናኟቸው ስመ ጥሩው ጀግና ፊታውራሪ ኃይሌ አባመርሳ ግን ሀሳቡን በመቃወም እኛ ለነፃነታችን እስከመጨረሻው ስለምንዋጋ ያለውን የጦር መሣሪያ ለኛ ያስረክቡን ቢሏቸውም በጅሮንድ ፍቅረ ሥላሴ ሳይስማሙ ስለቀሩ፤ ከነበጅሮንድ ጋር ተዋግተው ብዙ ሰው በውጊያው ከሞተ በኋላ ተማርከው ታሰሩ፡፡ በኋላም ጀግናው ፊታውራሪ ኃይሌ አባመርሳ ከእስር ቤት አምልጠው ከጠላት ጋር ጡርነት ገጥመው ሲዋጉ በጦርነቱ ላይ የሞቱ አገር ወዳድ ጀግና ነበሩ፡፡
Fitawurari Abebe Gebre
ፊታውራሪ አበበ ገብሬ
ለሐገሩ ነፃነትና ለመንግሥቱ ክብር ሲል አምስቱንም የጠላት ዘመን በአርበኝነት ያሳለፈና የመጀመሪያው የውስጥ አርበኛ መሥራች የነበረ፡፡
Fitawurari Kebede Yerdaw
ፊታውራሪ ከበደ ይርዳው
ከታላቁ የአርበኝነት ስራው በላይ በኢሉባቦር ጠቅላይ ግዛት “ሳምቢ” በተባለው ሥፍራ ከፋሽስት ወታደሮች ጋር ጦርነት ገጥሞ አንድ የዲቪዥን አዛዣ ኮሎኔልና እንዲሁም ቁጥራቸው 12‚786 የሚሆኑ የጣሊያን ወታደሮችን አንበርክኮ የማረከ ጀግና የጦር አርበኛ በመሆኑ ይህን የጀግንነት ሥራውን ትውልድ ሁሉ ሲያስታውሰው ይኖራል፡፡
Fitawurari Wodajo Gurmu
ፊታውራሪ ወዳጆ ጉርሙ
ዝነኛ ከሆኑት የመንዝ አርበኞች መካከል አንዱ
Fitawurar Nega Alemu
ፊታውራሪ ነጋ አለሙ
በአርበኝነት ሙያው እጅግ የተደነቀ
Kegnazmach Tadese Belayneh
ቀኛዝማች ታደሰ በላይነህ
ጭልፊትና የማይጨበጥ ጉም ሆኖበት ናላው እስኪዞር ድረስ ወራሪውን ጠላት ግራ ያጋባው ቀኛዝማች ታደሰ በላይነህ ይህ ነበር፡፡
Kegnazmach Yemane Berehan Abakoran
ቀኛዝማች የማነብርሀን አባኮራን
Gerazmach Reda Tesema
ግራዝማች ረዳ ተሰማ
ግራዝማች ረዳ ተሰማ የጭልጋ ባላባት ሲሆኑ፤ ንጉሠ ነገሥቱ ወደ ጎጃም በገቡበት ጊዜ፤ ከጭልጋ ወደ ሱዳን ተጠርተው ከሱዳን እስከ ማኅበረ ሥላሴ ድረስ ከጠላት አደጋ ለማዳን የሚያስችለውን መንገድ በቅንነትና በታማኝነት በመምራት ያገለገሉ የአርበኞች መሪ ነበሩ፡፡
Girazmach Abebe Kidane
ግራዝማች አበበ ኪዳኔ፣ ተክለሚካኤል ኪዳነማሪያም፣ ወልደጊዮርጊሰ ከለላው፣ ወንድምነህ ገብረ ኪዳን
የመንዝና ተጉለት አርበኞች
Shiferaw Bogale
ሽፈራው ቦጋለ
የመንዝ አርበኛ የነበረ
Ato Amdie Ferid
አቶ አምዴ ፈሪድ
ለአርበኞች ምግብ፣ መጠጥ፣ ልብስ፣ ጥይታና ሌላም መሣሪያ በማቀበል ከሚረዱ የውስጥ አርበኞች መካከል ለዕለት መተዳደሪያቸው እየሰሩ በሚያገኙት ገንዘብ፣ ምግብ፣ ልብስ፣ መድኃኒትና የጦር ሜዳ መነጽር እየገዙ ለአርበኞች ይልኩ የነበሩት አቶ አምዴ ፈሪድና ባለቤታቸው ወ/ሮ እሌኒ ይገኙባቸዋል፡፡
Ato Amenu Gebre
አቶ አመኑ ገብሬ
አቶ አመኑ ገብሬ ለሀገራቸው ያለባቸውን ግዴታ በመፈጸማቸው ለጊዜው ከነበረው ቤተክርስቲያን ከፍ ያለ ወቀሳና ተግሣፅ ቢደርስባቸውም፣ እንኳን በሀገሬ ሆኜ ሮማም ብሆን ለሀገሬ ማገልገሌን አላቋርጥም በማለት የሀገር ፍቅራቸውን ገልጠዋል፡፡
Ato Afework Adafre
አቶ አፈወርቅ አዳፍሬ
አምስት አመት ሙሉ ከፋሽስት ወታደሮች ጋር ሲዋጋ ቆይቶ ግርማዊነታቸው ከገቡ በኋላ ሞላሌ ላይ ሰፍሮ የነበረው የፋሽስት ጦር ባስቸገረበት ወቅት፣ በጦር ኃይል እንዲያዝ የተደረገ እንደሆነ የብዙ ሰው ሕይወት ያልቃል በማለት ያላንዳች ጦርነት በማስጠንቀቂያ ጽሁፍ ብቻ የፋሽስት ወታደሮች እጃቸውን ሰጥተው እንዲገቡ ያደረገ አርበኛ፣ አርበኛው አቶ አፈወርቅ አዳፍሬ ይህ ነው፡፡
Arbegna Feleke Ejigayehu
ፈለቀ እጅጋዬሁ
ከጀግንነት ሙያው የተነሳ ጠላትን በውን ቀርቶ በህልም ያስጨንቅ የነበረ የመረሐቤቴ ጀግና አርበኛ ከወንድሙ ከደምሴ እጅጋዬሁ እና ከጦር ጓደኞቹ ጋር፡፡
Aleka Mersha Woldemariam
አለቃ መርሻ ወልደማሪያም
ታላቁ አዛውንት አለቃ መርሻ ወልደማሪያም ፋሽስት ኢትዮጵያን ለመውረር በመጣ ጊዜ፣
"ወግጅልኝ ድጓ ወግጅልኝ ቅኔ፣
ወንዶች ከዋሉበት እውላለሁ እኔ፡፡”

በማለት ሦስት የፋሽስት ሹማምንቶችን ገድለው ልክ ጌታችን እየሱስ ክርሰቶስ በአይሁዶች እጅ በተሰቀለበት ዓርብ ዕለት ሐምሌ 10 ቀን 1928 በሰማዕትነት ሕየወታቸውን ለእናት ሀገራቸው አሰልፈው ሰጥተዋል፡፡
Belata Tesfamariam Nigiru
ብላታ ተስፋማርያም ንግሩ
በደሴ የኢጣሊያ ቆንስል ዋና ጸሐፊ ሆነው ይሠሩ በነበረበት ጊዜ ጣሊያን ኢትዮጵያን ለመውረር የነበረውን ዕቅድ በመግለጽና ፋሽስቶችም ኢትዮጵያን ከወረሩ በኋላ መጀመሪያ ከደጃዝማች ፍቅረማሪያም፣ ቀጥሎም ከልጅ ግዛቸው፣ በኋላም ከራስ አበበ አረጋይ ጋር እየተዘዋወሩ በአርበኝነት ሲዋጉ ቆይተው በጠላት ወታደሮች ተማርከው የሞት ፍርድ ተበይኖባቸው ነበር፡፡ በኋላም በአርበኝነት በነበሩበት ጊዜ በኢጣሊያንኛ ቋንቋ እየታተሙ ይወጡ የነበሩትን ጋዜጦች በአማርኛ እየተረጎሙ ለአርበኞች የሚያስረዱ የውስጥ አርበኛ ነበሩ፡፡
Basha Efrem Wolde
ባሻ ኤፍረም ወልዴ
ግንቦት 13 ቀን 1930 ዓ.ም. “ጠራ” ተብሎ በሚጠራው የውጊያ ቦታ ላይ ከጠላት ጋር በተደረገው ውጊያ በጀግንነት የወደቀ
Balambaras Gebremedehen Gosa
ባላምባራስ ገብረመድህን ጎሳ
Ato Asrat Yenesu
አቶ አሥራት ይነሱ
ድሬዳዋ ላይ ሆኖ ለሀገሩ በውስጥ አርበኝነት የሰጠው አገልግሎት እጅግ ከፍ ያለ ነው፡፡
Ato Teklu Delenesahu
አቶ ተክሉ ድልነሳሁ
በውስጥ አርበኝነት ያገለገሉ
Ato Haile Gebriel Negero
አቶ ኃይለ ገብርኤል ነገሮ
አቶ ኃይለ ገብርኤል ነገሮ የሀገርን ፍቅር እንደ እሳት ነበልባል በሆነ አንደበቱ የሰበከ፣ አምስቱን ዓመት በውስጥ አርበኝነት ተጋድሎ ግዳጁን የፈፀመ፣ የጠላት ገንዘብ ልቡን ማርኮ የሀገር ፍቅር አንደበቱን ሊድጠውና መሣሪያ ሊያደርገው ያልቻለ፣ ጠላት ብዙ ሺህ ገንዘብ በማፍሰስ አድኖ ይዞ ለመግደል ሳይሳካለት ቀርቶ እነሆ በነፃነት በሕይወት ኖሯል፡፡
Ato Gesses Tessema
አቶ ገሠሠ ተሰማ
የውስጥና የውጭ አርበኛ ሆኖ ሀገሩንና መንግሥቱን ያገለገለ፡፡
Ato Desta Alemie
አቶ ደስታ አለሜ
መጀመሪያ በቡልጋ በአርበኝነት፣ በኋላም ከተማ ገብተው በውስጥ አርበኝነት እያገለገሉ ፈጣሪያቸውን የኢትዮጵያን ነፃነት እንዲያሰጣቸው ዘወትር ይፀልዩ ነበር፡፡


Dejazmach Kebede Tesema
ክቡር ደጃዝማች ከበደ ተሰማ

በዚህ ድረገጽ የቀረቡት የተወሰኑት የአርበኞች ፎቶዎች ከነመግለጫቸው የተወሰዱት፣ በደጃዝማች ከበደ ተሰማ በ 1962 ዓ.ም. ታትሞ ከነበረው፤ “የአርበኞች ማስታዎሻ” ከተሰኘው መጽሐፍ ነው፡፡
ለተከበሩት ለዚህ መጽሐፍ ደራሲና ለቤተሰቦቻቸው በቅድሚያ ላቅ ያለ ምስጋና ለማቅረብ እንወዳለን፡፡
. . . የድረ ገጹ አዘጋጅ


የደጃዝማች ከበደ ተሰማ አጭር የሕይወት ታሪክ፤

ደጃዝማች ከበደ ተሰማ በ 1984 ዓ.ም. ከአባታቸው ከቀኛዝማች መንገሻ አያነህና ከእናታቸው ከወ/ሮ ደስታ ተሰማ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት፣ በመንዝና በይፋት አውራጃ፣ በኤፍራታ ወረዳ ሰቀልቲ ከተባለው ቀበሌ ተወለዱ፡፡
እድሜአቸው ለትምህርት እንደደረሰ የአማርኛ ትምህርት ተምረው በመንግሥት ሥራ ላይ ተሰማርተዋል፡፡


የአርበኝነት ዘመናቸውም ሲፈተሽ፤
  1. በማይጨው ጦር ሜዳ ውለው ሲዋጉ ቆስለዋል፡፡
  2. ከ 1932 ዓ.ም. እስከ 1933 ዓ.ም. ድረስ ጎጃም ውስጥ ከነበረው የጠላት ጦር ጋር ተዋግተዋል፡፡
  3. የፊታውራሪነት ማዕረግ ተሰጥቷቸው ወለጋ ከተመደቡ በኋላ ከጠላት ጦር ጋር ተዋግተዋል፡፡
  4. የኢትዮጵያን ነፃነት ለመመለስ ከእንግሊዝ መንግሥት ጋር በተደረገው ስምምነት በመጀመሪያ ጎጃም መጥተው ለኢትዮጵያ አርበኞች የነፃነት ብስራት ለማሰማት ብዙ ሰርተዋል፡፡
  5. ከነፃነት በኋላም በበርካታ የመንግስት የሥራ ዘርፎች ላይ በከፍተኛ የሥልጣን እርከን ላይ ተመድበው ከሕግ መምሪያ ምክር ቤት ፕሬዚዳንትነት እሰከ ዘውድ ምክር ቤት አባልነት አገልግለዋል፡፡

“ቀድሞ በአባቶቻችን የነበረውን ፍቅርና አንድነት እናድሰው እንጅ አናፍርሰው፡፡”

“አሁን መኖራችንን ብቻ አንመልከት፡፡ ፍቅርንና አንድነትን ይዘን ተባብረን መሥራት ከሌለ ነገ የለንም፡፡”

“ስንገናኝ በሽንገላ ምላስ፤ ወዳጅ መስሎ መታየት ለምንም የማይጠቅምና የማይረባ ሥራ ነው፡፡”



... ደጃዝማች ከበደ ተሰማ




Kegnazmach Tadese Zewolde
ቀኛዝማች ታደሰ ዘወልዴ
በዚህ ድረገጽ የቀረቡት የአርበኞች ፎቶዎች ከነመግለጫቸው በአብዛኛው የተወሰደው፣ በቀኛዝማች ታደሰ ዘወልዴ በ፲፱፻፰ ታትሞ ከነበረው፤
”ቀሪን ገረመው የአርበኞች ታሪክ” ከተሰኘው መጽሐፍ ነው፡፡
ለተከበሩት ለዚህ መጽሐፍ ደራሲና ለቤተሰቦቻቸው በቅድሚያ ላቅ ያለ ምስጋና ለማቅረብ እንወዳለን፡፡
...የድረ ገጹ አዘጋጅ


የአቶ ታደሰ ዘወልዴ አጭር የሕይወት ታሪክ

አቶ ታደሰ ዘወልዴ በ1895 ዓ.ም. ከአባታቸው ከአቶ ዘወልደ ማሪያም ሀብተ ማሪያምና ከእናታቸው ከወይዘሮ ወለተ ማሪያም በሸዋ ጠቅላይ ግዛት በመንዝና ይፋት አውራጃ ተወለዱ፡፡
በ1919 ዓ.ም. ወደ ግብፅ አገር ሄደው ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉ ከተመረጡት 21 ተማሪዎች ጋር እስክንደሪያ በመሄድ የፈረንሳይኛ ትምህርት ከተከታተሉ በኋላ ወደ ፈረንሳይ አገር ተጉዘው የቴሌኮሙኒኬሽን ትምህርት ሲማሩ እንደቆዩ በ1928 ዓ.ም. የጣሊያን ፋሽስት ወረራ በአገራችን ላይ ሲካሄድ የክተት አዋጁን በወዶዘማችነት ተቀብለው ወደ ሀገራቸው ተመልሰው ማይጨው ዘመቱ፡፡
አርበኛው ታደሰ ዘወልዴ፤ አርበኞች በቁጥራቸው ማነስ ሳይጨነቁ ችግሩን ሁሉ ተቋቁመው ለሀገራቸው ነፃነት በቆራጥነት እንዲዋጉ የሞራልና የመንፈስ ማበረታቻ ዘዴ በመጠቀም አስተዋጽኦ አድርገዋል፡፡


”አገሩን አፍቃሪ የሆነ ሰው ትግሉና ሩጫው ሁሉ ለትውልድ በሚሆን ነገር እንጅ ለራሱ በሚሆን ነገር ገንዘብና ርስት ለማግኘት በጠቅላላው ሀብት ለማድለብ ስላልሆነ ዛሬ በሞት የሚያልፈው ሰው የማይሞትና የማያልፍ ለትውልድ የሚሆን ነገር ሠርቶና ትቶ መሄድ አለበት፡፡”

”ሰው ከፍጥረታት ሁሉ በላይ ከፍ ያለ ፍጡር እንደመሆኑ መጠን አስተያዬቱ በግል ጥቅም የተወሰነና በዚህ ዓለምም የሚኖረው ራሱን ለማገልገል እንዳልሆነ ማወቅ ይኖርበታል፡፡“



...ቀኛዝማች ታደሰ ዘወልዴ - “ቀሪን ገረመው - የአርበኞች ታሪክ” ደራሲ