Content-Language: am ጥያቄና መልስ ገጽ ሁለት
header image


የሚያውቁትን ለማስታወስ እንዲረዳዎት ሳጥኑ ውስጥ ያሉትን ቀላል ጥያቄዎች አንብበው ለመመለስ ይሞክሩ የጥያቄውን መልስ ሳጥኑን በመጫን ያገኙታል


የተጫኑትን የጥያቄ ሳጥን ወደ ቀድሞው ቦታ ለመመለስ በድጋሚ ሳጥኑን ይጫኑት


ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ ምኒልክ ዘመነ መንግሥት
( ስለ ንግሥተ ነገሥታት ዘውዲቱ የበለጠ ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ)

1. በዐድዋ ጦርነት የገጠመውን ሀፍረት ለመሻር እና፣
2. እጅግ ለምና በከርሰ ምድር ሐብቷ የበለፀገችውን ኢትየጵያን ለመቆጣጠር ነበር፡፡

እንግሊዝ

መስከረም 22 ቀን 1928 ዓ.ም.

ደጃዝማች ኃይለ ሥላሴ ጉግሳ ይባላል፡፡
ኃይለ ሥላሴ ጉግሳ፤ ከአፄ ዮሐንስ የልጅ ልጅ የሚወለድ ሲሆን ባለቤቱም የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ሁለተኛ ልጅ ልዕልት ዘነበወርቅ ነበሩ፡፡

Haile Selassie Gugsa
ከሃዲው ኃይለሥላሴ ጉግሣ
ኃይለ ሥላሴ ጉግሳ በተሰጠው ማዕረግ ደስተኛ ስላልነበረ ቂም መቋጠሩን የተረዱት የኢጣሊያ አዛዦችም ከራስ ስዩም መንገሻ ነጥቀን ሙሉ ትግራይን እንሰጥሀለን ብለውት ስለነበረ ይህን ተሰፋ አድርጎ ከጠላት ጋር ወግኖ አገሩን ሲወጋ ቆይቶ በኋላም ጣሊያኖች የተመኘውን የራስነት ማዕረግ ብቻ ሰተውት ነበር፡፡
ጣሊያኖች ኢትዮጵያን ለቀው ከወጡ በኋላ ግን በአገር ክህደት ወንጀል ተከሶና የተሠጠውም የራስነት ማዕረግ ተገፎ ለብዙ ዘመናት በእስር ቤት ከቆየ በኋላ ሕይወቱ አልፏል፡፡

12 ሚሊዮን

ዶክተር መላኩ በያን ይባላል፡፡
Dr. Melaku Beyan
ዶክተር መላኩ በያን
ዶክተር መላኩ በያን የተወለደው በወሎ ጠቅላይ ግዛት ሲሆን በ30 ዓመት እድሜው ወደ አሜሪካ ለትምህርት ተልኮ ዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው ዝነኛና ታዋቂ ከሆነው አፍሪካ አሜሪካዉያን ከሚማሩበት ከሃዋርድ ዩኒቨርሲቲ በሕክምና ዶክትሬት ዲግሪ የተመረቀ ብቸኛውና የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ የሕክምና ዶክተር ነበር፡፡
ዶክተር መላኩ፤ በአሜሪካ ምድር “የኢትዮጵያ የዓለም ፌደሬሽን” የተሰኘውን ድርጅት በኒውዮርክ ከተማ ነሐሴ 19 ቀን 1929 ዓ. ም. በመመስረት ታላቅ ተግባር የፈፀመ እውቅ ኢትዮጵያዊ ምሁር ነበር፡፡

( ስለ ንዶክተር መላኩ በያን የበለጠ ለማንበብ) ይህን ሊንክ ተጭነው ክፍል 19ን ያንብቡ

ኢምፔሪያል ኢትዮጵያ አቪየሽን (Ethiopian Imperial Aviation)

ኮሎኔል ስምረት መድኃኔ ይባላሉ፡
Col. Semeret Medehane
ኮሎኔል ስምረት መድኃኔ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ታህሳስ 12 ቀን 1938 ዓ. ም. ከተቋቋመ ጊዜ ጀምሮ ሙሉ በሙሉ በአሜሪካኖች ይመራ ነበር፡፡
ከ26 ዓመታት ቆይታ በኋላ ኮሎኔል ስምረት መድኃኔ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሆነው ተሾሙ፡፡
የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ አባት ልዑል ራስ መኮንን ወልደ ሚካኤል ይባላሉ::
(ስለ ልዑል ራስ መኮንን ወልደ ሚካኤል የበለጠ ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ)
Ras Mekonnen Wolde Michael
ልዑል ራስ መኮንን ወልደ ሚካኤል
ቀዳማዊ ምኒልከ
Kedamawi Menilk
በአክሱም ፅዮን የሚገኘው
የቀዳማዊ ምኒልክ ስዕል
በአክሱሙ ንቡረዕድ ይስሐቅ በ14ኛው ክፍለ ዘመን በግዝ ቋንቋ በተጻፈው ክብረ ነገሥት ላይ እንደተመዘገበው የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ንጉሥ ምኒልክ ከንጉሥ ሰለሞንና ከንግሥተ ሳባ የተወለደ ነው፡፡
ንጉሥ ሰለሞን የቃል ኪዳኑን ታቦት ለልጁ ለምኒልክ በስጦታ ከሰጠው በኋላ ምኒልክ በርካታ እስራኤላውያንን አስከትሎ ወደ ሀገሩ ወደ ኢትዮጵያ ከተመለሰ በኋላ እናቱ ንግሥት ሳባ ስትሞት በአንድ ሺህ ዓመተ ዓለም ዘውዱን ድፍቶ ቀዳማዊ ምኒልክ ተብሎ ለኢትዮጵያ የመጀመሪያው ንጉሥ መሆን ቻለ፡፡
ቀዳማዊ ምኒልክ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ከሆነ በኋላ “የመጀመሪያውን ሰለሞናዊ ሥርዎ መንግሥት” (Solomonic Dynasty) መሠረተ፡፡
ከቀዳማዊ ምኒልክ ጀምሮ ለ 3ሺህ ዘመናት የቆየው ሰለሞናዊው ሥርዎ መንግሥት፤ ደርግ በ1966 ዓ. ም. በመፈንቅለ መንግሥት ሥልጣን ሲረከብ፤ 225ኛው የ ሰለሞናዊው ስርዎ መንግሥት የመጨረሻ ፍጻሜው ሆነ፡፡

(ስለ ዳግማዊ አፄ ምኒልክ የበለጠ ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ) ዳግማዊ አፄ ምኒልክ

(ስለ ግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ የበለጠ ለማንበብ ይህን ሊንክ ይጫኑ) ግርማዊ ቀዳማዊ ኃይለሥላሴ
ዶክተር ስንዱ ገብሩ ይባላሉ፡፡
Dr. Senedu Gebru
ዶክተር ስንዱ ገብሩ
ዶክተር ስንዱ፤ በውጥጭ አገር ትምህርት የቀሰሙ ሲሆን የታሪክ፣ የእንግሊዝኛና የፈረንሳይኛ ቋንቋዎችን ተምረዋል፡፡
የስንዱ ገብሩ ወላጅ አባት ከንቲባ ገብሩ፤ ታዋቂ ዲፕሎማት፣ የመጀመሪያው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምክትል ፕሬዝደንት፤ ኢጣሊያ ከኢትዮጵያ ለቃ ከወጣችም በኋላ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፕሬዝደንት፤ በዳግማዊ ምኒልክ ጊዜም የመጀመሪያው የጎንደር አስተዳዳሪ ሆነው ያገለገሉ ናቸው፡፡
የከንቲባ ገብሩ ታናሽ እህት የውብዳር ገብሩ ይባላሉ፡፡ ከመነኮሱም በኋላ እማሆይ ጽጌ ማሪያም ተባሉ፡፡
ነጋድራስ ተሰማ እሸቴ ይባላሉ፡፡
Tessema Eshete
ነጋድራስ ተሰማ እሸቴ
ሐምሌ 20 ቀን 1869 ዓ. ም. ምንጃር የተወለዱት ነጋድራስ ተሰማ እሸቴ፤ ከዓድዋ ድል በኋላ በሁለተኛው ዓመት ጀርመን አገር ተልከው የመጀመሪያ የሆነውን መዲናና ዘለሰኛ የያዘ የአማርኛ ዜማ በሸክላ ከአስቀረፁ በኋላ ሸክላውን ያስቀረፀው ኩባንያ የድካምዎ ዋጋ ይሁንዎ ብሎ የሰጣቸውን 16 ሺህ የጀርመን ፍራንክ ተቀብለው ወደ አገራቸው ተመልሰዋል፡፡
ነጋድራስ ተሰማ እሸቴ የብዙ ሙያዎች ባለቤት በመሆናቸው፤ ገጣሚ፣ ጥበበኛ፣ ሰዓሊ፣ ቀራፂ፣ የፖለቲካ ሹም፣ አሳሽና የተዋጣለት ፎቶግራፍ አንሺ እንደነበሩ ተዘግቧል፡፡ ነጋድራስ ተሰማ እሸቴ በ88 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡
የነጋድራስ ተሰማ እሸቴ ልጅ የነበሩት አቶ ይድነቃቸው ተሠማ፤ በቅዱስ ጊዮርጊስ የእግር ኳስ ክለብ ለ27 ዓመታት የተጫወቱ፣ የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽንን ከአቋቋሙት ውስጥ አንዱ የሆኑ፣ የእግር ኳስን ሕግ ወደ አማርኛ የተረጎሙ፤ የዓለም አቀፍ ኦሎምፒክ ኮሚቴና የፊፋ አባል የነበሩና በመጨረሻም የአፍሪካ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፕሬዝዳንት የነበሩ ናቸው፡፡
የኢትዮጵያና ብሎም የአፍሪካ የዘመናዊ ስፖርት አባት የተባሉት አቶ ይድነቃቸው ተሠማ ነሐሴ 14 ቀን 1979 ዓ. ም. በተወለዱ በ66 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡
ነጋድራስ ተሰማ እሸቴ በ 1900 ዓ. ም. ካሳተሙት የሙዚቃ ሸክላ የተወሰደውን የ 1 ደቂቃ ሙዚቃ ቀጥለው ያዳምጡ፡፡

( ምስጋና ለ፤  Ibex Media)
እማሆይ ፅጌ ማሪያም ገብሩ ይባላሉ፡፡
Emahoy Tsigemariam
እማሆይ ፅጌ ማሪያም ገብሩ
እማሆይ ፅጌ ማሪያም ከመመንኮሳቸው በፊት የውብዳር ገብሩ ይባሉ ነበር፡፡ የዶክተር ስንዱ ገብሩ እህት ናቸው፡፡
ገና በ19 ዓመት ለጋ እድሜያቸው ከቤተሰቦቻቸው ጠፍተው ወደ ግሸን ማርያም በመሄድ ምንኩስና ተቀብለዋል፡፡
እየሩሳሌምም ለ30 ዓመታት ያህል ኖረዋል፡፡ እማሆይ ፅጌ ማርያም 99ኛ ዓመታቸውን አክብረው 100ኛ ዓመታቸውን እንደያዙ ይነገራል፡፡

ዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ

ዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ

በዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ

ዳግማዊ አፄ ምኒልክ
( ስለ ዳግማዊ አፄ ምኒል የበለጠ ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ)

እቴጌ ጣይቱ ሆቴል
እቴጌ ጣይቱ ሆቴል፤ ከዓድዋ ድል ከ10 ዓመት በኋላ በ1998 ዓ. ም. አሁን ፒያሣ ተብሎ በሚጠራው ስፍራ ከተሠራ በኋላ እቴጌ ጣይቱ ራሳቸው እያሰተናገዱና በነፃም እየጋበዙ ተጋባዥ እንግዶችን የሆቴል አገልግሎት እንዳለማመዱ ተዘግቧል፡፡
(ስለ እቴጌ ጣይቱ የበለጠ ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ) እቴጌ ጣይቱ

ጀነራል አለልቤርቶኒ ይባላል፡፡
በዓድዋ ጦርነት ወቅት ፋሽስት ኢጣሊያ ያሰለፈቻቸው ጀነራሎች ከዋናው አዛዥ ጋር አምስት ሲሆኑ ስማቸውም፤
Albertoni
በኢትዮጵያውያን የተማረከው
ጀነራል አልቤርቶኒ

1. ጀነራል ባራቲዬሪ - ዋና የጦር አዛዥ፣
2. ጀነራል አሪሞንዲን፣
3. ጀነራል ዳቦር ሜዳ፣
4. ጀነራል አለልቤርቶኒ እና
5. በወቅቱ አዲስ ሹመት አግኝቶ የነበረው ጀነራል ኤሌና ይባላሉ፡፡